ስለ ኢትዮ ቴሌኮም

አጭር ታሪካዊ ዳራ

የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት በኢትዮጵያ የተጀመረው በዳግማዊ ሚኒሊክ ዘመነ መንግሥት በ1886 ዓ.ም. ከሐረር ከተማ ወደ ሐገሪቷ ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ በተዘረጋው የቴሌፎን እና ቴሌግራፍ መስመር አማካኝነት ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ የስልክ መገናኛ መስመሮች ከዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በሁሉም አቅጣጫዎች እየተስፋፉ በመሄዳቸው በርካታ የአገሪቷ ዋና ዋና ከተሞች በኦፕሬተሮች አማካይነት የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን በቅተዋል፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም አመሠራረት

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ መንግሥት ከ1998-2002 ዓ.ም. የተነደፈውን የአምስት ዓመት እቅድ በማስቀጠል እንዲሁም ጥረቱን በትምህርት፣ በጤናና በግብርና ላይ ትኩረት ከመስጠት ባሻገር የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ለሀገራችን ሁለንተናዊ ልማት ወሳኝ ኃይል መሆኑን በመገንዘብና አገልግሎቱን ለማሻሻል በመወሰን የሀገራችንን ቀጣይ እድገት ለማገዝ ካለው ፍላጎት አኳያ ኢትዮ ቴሌኮም ሕዳር 21 ቀን 2003 ዓ.ም በአዲስ ስያሜና በአዲስ መልክ እንዲመሠረት ተደርጓል፡፡

መዋቅራዊ አደረጃጀት (በተለያዩ ጊዚያት ከተሰጡ አዳዲስ ስያሜዎች ጋር)

  • 1886 ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ የቴሌፎንና የቴሌግራፍ ማዕከላዊ አስተዳደር
  • 1900 ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ የፖስታ፣ ቴሌግራፍ እና ቴሌፎን ማዕከላዊ ቢሮ
  • 1903 ዓ.ም፡- የፖስታ፣ የቴሌግራፍ እና ቴሌፎን ሚኒስቴር (ፖቴቴ)
  • 1945 ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ቴሌኮሙኒኬሽን ቦርድ

(የድርጅቱን የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት የሥራ መደቦች በወጣት ኢትዮጵያዊያን የመተካት መርሐ ግብር በ1960 ዓ.ም ተከናውኖ ተጠናቀቀ) ፤በተለያዩ ጊዚያት የተሰጡ አዳዲስ ስያሜዎችም የሚከተሉት ናቸው፡-

  • 1967 ዓ.ም:- የሶሻሊስት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ድርጅት
  • 1989 ዓ.ም:- የኢትጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን
  • 2003 ዓ.ም:- ኢትዮ ቴሌኮም

ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ሽግግር

የፌደራል መንግስት የቴሌኮም አገልግሎቶችን ለአገራዊ ልማት ቁልፍ ወስዶ በትኩረት እንዲሰራ መወሰኑን ተከትሎ ኢትዮ ቴሌኮም ከህዳር 29 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ አሁን ያለበትን ደረጃ አግኝቷል። በዚህም የሀገሪቱን የቴሌኮም መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ወደ ዓለም አቀፍ ደረጃ በመቀየር በዘርፉ መሻሻል ላይ ትልቅ ለውጥ በማድረግ የሀገሪቱን ልማት ለማሳለጥ ተችሏል።

የቴክኖሎጂ ዕድገት

የ5G ኔትወርክ በይፋ አገልግሎት ማስጀመር

በአዲስ ተስፋ እና እይታ ወደ አዲስ ፍጥነት፣ አዲስ ምቾት እና አኗኗር የሚያሸጋግረን፣ ለማህበረሰባችን በርካታ ትሩፋቶችን የሚያበረክተው እና የቢዝነስ እንቅስቃሴን የሚያቀላጥፈውን  የዘመናችን የመጨረሻውን የ5G ኔትወርክ ለህዝባችን በአዲስ ዓመት ስጦታነት ማበርከታችንን አብስረናል!

2020

5G የሞባይል ቴክኖሎጂ

ኩባንያችን ይህንን ቴክኖሎጂ በሀገራችን ዋና ከተማ እንዲሁም የዓለም አቀፍና አህጉራዊ ዲፕሎማቲክ ከተማ በሆነችው አዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ እውን ማድረጉ ተመራጭ የቴሌኮም ኦፕሬተር ነው፡፡

2020

ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ አገልግሎት

ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት በ2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ቦታዎች አገልግሎት መስጠት ጀመረ

2020

4ጂ/ኤል.ቲ.ኢ

የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አገልግሎት በ2007 ዓ.ም  በአዲስ አበባ በተመረጡ ቦታዎች  ተጀመረ::

2015

ኤን ጂኤን ፣3ጂ እና ዲደብሊውዴኤም

የቀጣዩ ትውልድ መደበኛ፣ሶስተኛው ትውልድ ኔትወርክ እና ዲደብሊውዴኤም በኦፕቲካል ፍይበር መጀመር

2007

ብሮድባንድ መልቲ ሚዲያ አገልግሎት

የብሮድባንድ መልቲ ሚዲያ አገልግሎት በ1996 ዓ.ም ተጀመረ

2004

የሮሚንግ አገልግሎት

የሮሚንግ አገልግሎት በ1995 ዓ.ም ተጀመረ

2003

የሞባይል /ተንቀሳቃሽ/ ስልክ አገልግሎት

የሞባይል /ተንቀሳቃሽ/ ስልክ አገልግሎት በ1991 ዓ.ም ተጀመረ

1999

የኢንተርኔት አገልግሎት

የኢንተርኔት አገልግሎት በ1989 ዓ.ም አገልግሎት ላይ እንዲውል ተደረገ::

1997

የዲጂታል ማይክሮዌቭና ፋይበር ኬብል መገናኛ ዘዴ

የዲጂታል ማይክሮዌቭና የፋይበር ኬብል መገናኛ ዘዴዎች በ1981 ዓ.ም ተጀመረ::

1989

ዲጂታል ማዞሪያ

የዲጂታል ማዞሪያ በ1980 ዓ.ም እንዲቋቋም ተደረገ::

1988

የምድር ሳተላይት ጣቢያ

  • በሱሉልታ የምድርሳተላይት ጣቢያ አማካኝነት ዓለምአቀፍግንኙነትተጀመረ

በሦስት የተለያዩ አቅጣጫዎች የተተከሉ ጣቢያዎች

  • በ1971 ዓ.ም: - ትልቁና 32 ሜትር ሬዲየስ ስፋት ዲሽ ያለው የሱሉልታ የምድር ሳተላይት መገናኛ አውታር ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
  • በ1980 ዓ.ም: - ሁለተኛውና 13 ሜትር ሬዲየስ ስፋት ዲሽ ያለው የሱሉልታ የምድር ሳተላይት መገናኛ አውታር ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
  • በ1993 ዓ.ም: - ሦስተኛውና 3 ሜትር ሬዲየስ ስፋት ዲሽ ያለው የሱሉልታ ባለዲጂታል የምድር ሳተላይት መገናኛ አውታር ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ::

1979 -1987

የዓለም አቀፍ እና አገር ውስጥ የሬዲዮ ጣቢያ አገልግሎቶች

ለዓለም አቀፍ እና አገር ውስጥ መገናኛ አገልግሎቶች የሚውሉ የሬዲዮ ጣቢያዎች በ1944 ዓ.ም እንዲቋቋሙ ተደርጎ አገልግሎት መስጠት ጀመሩ::

1952

የቴሌግራፍ አገልግሎት

የድሬዳዋ - ጅቡቲ ቴሌግራፍ መስመር ዝርጋታ ሥራ ተጠናቆ በ1898 ዓ.ም አገልግሎት ተጀመረ::

1906

የረጅም ርቀት የድምፅ ጥሪ አገልግሎት በኦፕሬተር አማካኝነት መስጠት

የረጅም ርቀት የድምፅ ጥሪ አገልግሎት በኦፕሬተር አማካኝነት መስጠት

1894

የኩባንያችን ተልዕኮ፣ ራዕይ እና እሴቶቻችን

እንቅስቃሴ በማሳለጥ አካታች እድገት እንዲኖር የማስቻል ራዕይ የሰነቀ LEAD (መሪ) የተሰኘ የሦስት ዓመት የእድገት ስትራቴጂ ቀርጾ እ.ኤ.አ ከሐምሌ 01 ቀን 2022 ጀምሮ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ ይህም በውድድር ገበያው በሁሉም መስክ የመሪነት ሚና በመጫወት የሀገራችን የቴሌኮም ዘርፍ የማህበረሰባችን ሁለንተናዊ እድገት ላይ አዎንታዊ አስተዋጽዖ እንዲኖረው የማስቻል ታላቅ ዓላማን ያነገበ ነው፡፡

አስተማማኝ የኮሙኒኬሽን እና የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት በማቅረብ ሕይወትን ማቅለል እና የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን

ተልዕኮ

መሪ የዲጂታል አገልግሎት አቅራቢ

ራዕይ

1. ሰው ተኮር

    • ከሰራተኞቻችን ፣ ከደንበኞቻችን እና ከባለድርሻ አካላትን ፍላጎት እና እሴቶች ጋር የተጣጣመ አገልግሎት መስጠት

2. ታማኝነት

    • የቢዝነስ ስራዎችን ስንሰራ ታማኝነትን፣ ሀላፊነትን እና ተጠያቂነትን ማዕከል ያደረገ እንዲሁም ስነ-ምግባርን የተላበሰ ስራ መስራት

3. ልህቀት

    • ለጥራት፣ ለልህቀት እና ለሙያ ቁርጠኛ መሆን እያንዳንዱን ተግዳሮቶች እንደ እድል በመውሰድ ዲጂታል ላይ ያተኮሩ አዳዲስ ፈጠራዎችን እና አሰራሮችን በመተግበር የተሻለ ውጤት ማምጣት

4. ማህበራዊ ሃላፊነት

    • አካባቢያችን እንከባከባለን፣ እንጠብቃለን፣ ለህብረተሰባችን ሁለንተናዊ እድገት አስተዋጽኦ እናደርጋለን፣ ስራዎቻችን በሥነ-ምግባር እና በሃላፊነት እንሰራለን።

5. አብሮነት

    • ስራችን በጋራ እና በቡድን ከሥነ-ምህዳሩ ተዋናዮች ጋር በትብብር መስራት እና አብሮ ለማደግ እንሰራለን

እሴት

አስተማማኝ የኮሙኒኬሽን እና የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት በማቅረብ ሕይወትን ማቅለል እና የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን

መሪ የዲጂታል አገልግሎት አቅራቢ

ሰው ተኮር

ከሰራተኞቻችን ፣ ከደንበኞቻችን እና ከባለድርሻ አካላትን ፍላጎት እና እሴቶች ጋር የተጣጣመ አገልግሎት መስጠት

ታማኝነት

የቢዝነስ ስራዎችን ስንሰራ ታማኝነትን፣ ሀላፊነትን እና ተጠያቂነትን ማዕከል ያደረገ እንዲሁም ስነ-ምግባርን የተላበሰ ስራ መስራት

ልህቀት

ለጥራት፣ ለልህቀት እና ለሙያ ቁርጠኛ መሆን እያንዳንዱን ተግዳሮቶች እንደ እድል በመውሰድ ዲጂታል ላይ ያተኮሩ አዳዲስ ፈጠራዎችን እና አሰራሮችን በመተግበር የተሻለ ውጤት ማምጣት

ማህበራዊ ሃላፊነት

አካባቢያችን እንከባከባለን፣ እንጠብቃለን፣ ለህብረተሰባችን ሁለንተናዊ እድገት አስተዋጽኦ እናደርጋለን፣ ስራዎቻችን በሥነ-ምግባር እና በሃላፊነት እንሰራለን።

አብሮነት

ስራችን በጋራ እና በቡድን ከሥነ-ምህዳሩ ተዋናዮች ጋር በትብብር መስራት እና አብሮ ለማደግ እንሰራለን